Events

Events የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

image description
Start Date icon
End Date icon
Location አደዋ 00 ፓርክ

በዓለም ለ21ኛ ግዛት በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው እልም እቅፍ የፀረ ሙስና ቀን ከተማ አቀፍ የማጠናቀቂያ ስነ ስርዓት በአድዋ መታሰቢያ አዳራሽ በድምቀት ተካሄደ፡፡

 

በማጠናቀቂያ ስነ ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በፀረ ሙስና ትግሉ ላይ በተደረጉ ጥረቶች በርካታ ውጤቶች እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።

የፀረ ሙስና ትግሉ የሚጀምረው ማህበረሰቡ ስለሙስና ያለውን አመለካከት በመቀየርና ግንዛቤ በማሳደግ ነው ያሉት ከንቲባዋ የግንዛቤ ፈጠራና የስብዕና ቀረፃ ስራው የሚጀምረው ከቤተሰብ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማትና ትምህርት ቤቶችም የማይተካ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።

 

አክለውም "ወጣቶች የነገ ተስፋችሁና ህልማችሁ እንዳይሰረቅ ሙስናን መታገል አለባችሁ" ያሉ ሲሆን ሁሉም ማህበረሰብ በተቀመጠለት የትግል አቅጣጫ ውስጥ ገብተው እንዲታገሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀማል ረዲ በበኩላቸው የማህበረሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የፀረ ሙስና ቀን በየዓመቱ በተለያዩ መሪ ቃሎች እንደሚከበር ገልፀው የዘንድሮው "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ ሙስና ትግል የነገ ስብዕና ይገነባል" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል ብለዋል። ሙስና በማህበረሰቡ በተለይም ደግሞ በወጣቶች ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት ኮሚሽነሩ ወጣቶች ህልማቸውን እንዳይኖሩ የሚያደርግ በመሆኑ በጋራ ልንታገለው ይገባል ብለዋል።

 

በማጠናቀቂያ ስነ ስርዓቱ ላይ 21ኛውን አለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በከተማ አቀፍ ደረጃ በድምቀት እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ ተቋማት የዕውቅናና የምስጋና ስነ ስርዓት ተካሂዷል።

“ሙስና ስጋት የማይሆንባት አዲስ አበባን እንፈጥራለን!”


Related Events

image description
የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

  • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
More Details
image description
የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

  • አዲስ አበባ ባህልና ቲያትር አዳራሽ
More Details
image description
የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

  • በወዳጅነት ፓርክ
More Details
image description
የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

  • አደዋ 00 ፓርክ
More Details
image description
የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

  • አደዋ 00 ፓርክ
More Details